የቁስቋም ጣይቱ ብጡል የመጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች የዘውዲቱ መሸሻ የህጻናትና ቤተሰብ የበጎ አድራጎት ልማት ማህበርን ጋር ምክክርና ጉብኝት አደረጉ፡፡

By adminzewd

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17/2018 ዓ.ም የቁስቋም ጣይቱ ብጡል የመጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች የዘውዲቱ መሸሻ የህጻናትና ቤተሰብ የበጎ አድራጎት ልማት ማህበርን በአካል በመጎብኘት የተለያዩ የልማት እና የህጻናት ድጋፍ ሥራዎችን ተመልክተዋል። በዚሁ ውይይት ወቅት የድርጅቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ቀሲስ አበባየሁ ፍቃዱ በሰጡት ገለጻ፣ ድርጅቱ እንዴት እንደተመሰረተ፣ በየደረጃው ያለፈባቸውን ሂደቶች እና በአሁኑ ወቅት ያለበትን ሁኔታ…

ለማዕከሉ ህፃናት በበጎ ፈቃደኛ የህክምና ባለሙያዎች የጤና ምርመራ ተካሄደ

By adminzewd

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14/2018 ዓ.ም የዘውዲቱ መሸሻ የህጻናትና ቤተሰብ የበጎ አድራጎትና ልማት ማህበር በሽሮሜዳ ቁስቋም ለሚገኙ ዕድሜያቸው ከ12 ዓመት በታች ለሆኑ የማዕከሉ ህፃናት የጤና ሁኔታ ለማሻሻል ያለመ የጤና ምርመራና የምክር አገልግሎት በበጎ ፈቃደኛ ዶክተሮች መጋቢት 12/2018 ዓ.ም ተከናውኗል። በዚህ ፕሮግራም የህፃናቱ የጤና ምርመራ አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን፣ የእድገት እና የአመጋገብ ሁኔታቸውም ምርመራ ተደርጎላቸዋል። ከምርመራው ጎን ለጎን…

እናመሰግናለን

By adminzewd

​ኢትዮ ቴሌኮም በሀገራችን ካሉ ግንባር ቀደም እና ጠንካራ ተቋማት አንዱ እንደመሆኑ መጠን፣ በንግድ ስራው ዘርፍ ብቻ ሳይሆን ማህበራዊ ሃላፊነቱንም በከፍተኛ ስሜት እንደሚወጣ በተግባር አሳይቷል። ይህንን ለማረጋገጥ ደግሞ ለእመበረከት ዘውዲቱ መሸሻ የህፃናት ማሳደጊያ ማዕከል እያደረገ ያለው ድጋፍ እንደ ማሳያ ሊጠቀስ ይችላል። ​የዘውዲቱ መሸሻ የህፃናት ማሳደጊያ ለበርካታ ዓመታት የነገ ተስፋ ለሆኑ ህፃናት በፍቅር፣ በእንክብካቤ እና በጤንነት እንዲያድጉ…

የዓለም ባንክ

By adminzewd

የዓለም ባንክ የሥራ አላፊዎች የዘውዲቱ መሸሻ የሕጻናትና ቤተሰብ የበጎ አድራጎትና ልማት ማኅበርን ጎበኙ የዓለም ባንክ የሥራ አላፊዎች ህዳር 26/2017 ዓ.ም ቁስቋም አካበቢ የሚገኘው ማዕከል በአካል ተገኝተው ጉብኝት አድርገዋል፡፡ በጉብኝታቸውም የእማማ ዘውዲቱን ያለፉት 35 ዓመታት የሠሩት ሥራ በአካል ተገኝተው መመልከታቸው እንዳስደሰታቸው በመግለጽ የዓለም ባንክ በቀጣይ ሰራተኞቹን ሁሉ ይዞ በመምጣት እንደሚጎበኛቸው ቃል ገብተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የእማማ ዘውዲቱ…

እማማ ዘውዲቱ ድርጅት ውስጥ ያደጉ አራት ልጆችን አስመረቀ

By adminzewd

የእማማ ዘውዲቱ ድርጅት ጥቅምት 6/2015 ዓ.ም በድርጅቱ ውስጥ ያደጉ አራት ልጆችን አስመረቀ በዕለቱ ከተለያዩ ተቋማት የተመረቁት ተማሪዎች 2 በማስተርስ 2 ደግሞ በዲፕሎማ የተመረቁ ናቸው ተማሪዎቹ በምረቃቸው ወቅት ለእዚህ ክብር ያበቃቸውን የእማማ ዘውዲቱ እና የድርጅቱን ድካም አቅም በፈቀደ ሁሉ ለመመለስና ሀገራቸው በመጥቀም ብድራቸውን ለመመለስ እንደሚተጉ ተናግረዋል።